ገ ረ ገ ራ     በማንኛዉም የመጽሐፍ አዟሪና መደብር ይገኛል።     Order4Delivery (እዚሁ ያዝዙ)
የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር

“ማኅደረ ደራስያን” እና ሌሎች መጽሐፍት ደራሲ

የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር

[የትዉልድ ቀን] 0000-00-00
[አጭር መግለጫ]

ኢ.ደ.ማ.፣ በእውቅ ሰዎች እና ደራስያን ሲመራ እና ሲስተዳደር ቆይቷል። ማኅበሩን ካቋቋሙት ደራስያን መካከልም ደጃዝማች ግርማቸው ተክለ ሐዋርያት፣ ብላታ ወልደ ጊዮርጊስ ወልደ ዮሐንስ፣ አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ (የኢፌዲሪ ፕሬዚዳንት)፣ ጸሐፌ ተውኔት መንግስቱ ለማ፣ አቤ ጉበኛ፣ ሎሬት ጸጋዬ ገብረ መድህን፣ ለማ ፈይሳ፣ ከበደ ሚካኤልና ጳውሎስ ኞኞን የመሳሰሉት በቀዳሚነት ይጠቀሳሉ። ቀዳሚ የማኅበሩ ርዕስ ክቡር ራስ ቢትወደድ መኮንን እንዳልካቸው (በዝነኛው “አልሞትኩም ብዬ አልዋሽም” ድርሰታቸው ይታወቃሉ) ሲሆኑ ቀጥለውም ደጃዝማች ግርማቸው ተክለ ሐዋርያት ማሕበሩን መርተዋል። ብላታ ጌታዬ አስፋው ተፈራም በጸሐፊነት ተመርጠው አገልግለዋል። ማኅበሩን በልዩ-ልዩ ሥልጣነ-ወንበር ካገለገሉት ሌሎች ደግሞ በከፊሉ፦ አቶ አምደ ሚካኤል ደሳለኝ፣ አቶ ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ፤ አሰፋ ገብረ ማርያም፣ ደበበ ሰይፉ፣ ማሞ ውድነህ እና አሁን በፕሬዝዳንትነት እየመሩት ያሉት ጌታቸው በለጠም ይገኙበታል።

"የኢትዮጵያ ድርሰት ማኅበር (ኢደማ) ተብሎ የተቋቋመው ይህ ድርጅት፣ መጠሪያውን በ፲፱፻፸ ዓ.ም. ወደ “የኢትዮጵያ ደራስያን አንድነት ማኅበር” ከለወጠው በኋላ፣ ያሁኑን መደበኛ መጠሪያውን “የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር” (ኢደማ) ያገኘው የካቲት ፲፩ ቀን ፲፱፻፸፰ ዓ.ም. ነው።
በቅርቡ በ"ፍኖተ ነፃነት" ጋዜጣ ላይ ማኅበሩን ከመሠረቱት እና በጸሐፊነትም ካገለገሉት ከብላታ ጌታዬ አስፋው ተፈራ ጋር በተደረገ ቃለ-ምልልስ እንደተዘገበው፤- ማሕብሩ ሲመሠረት በዋናነት ዓላማው አድርጎ የተነሣው «በሀገሪቷ ያሉት የጽሑፍ ቅርሶች በዋናነት ተሰባስበው እንዲታተሙና ሌሎች አዳዲስ ጸሐፍትን ለማፍራት» እንደነበር እና «የአሁኑ የሀገሪቷ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደ ጊዮርጊስ የደራስያን ማኅበሩ ገንዘብ ያዥ በነበሩበት ጊዜ መንግሥት የመጽሐፍ ህትመትን ወጪ ¼ኛ እንዲሸፍን» አድረገዋል። ብላታ ጌታዬ አስፋው ቀጥለውም፣ «ይኸንኑ ¼ መንግሥት ይሸፍነዋል የሚባለውን ወጪ ብርሃንና ሰላም ማተሚያ ቤት ሕትመቱን ካከናወነ በኋላ ያልተሸጠውን ትምህርት ሚኒስቴር እንዲገዛው ተደርጐ ትምህርት ቤቶች ለሪፈረንስ (ማጣቀሻ) እንዲጠቀሙበት ይደረጋል።» ብለዋል። ንጉሠ ነገሥቱም ቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ «ለመጽሐፍ ትልቅ ፍቅር ስለነበራቸውና አርአያ ለመሆን ቲያትርን እንደሚመለከቱና እንደሚገመግሙ ሁሉ ወመዘክር (ብሔራዊ ቤተ-መዛግብትና መጽሐፍት ማዕከል) በመገኘት በመጽሐፍ ሂስና ውይይት ላይ ይካፈሉ እንደነበር» ብላታ ጌታዬ አስፋው ተፈራ ገልጸዋል። ከዚህም ሌላ የብላታ ጌታዬ ትውስታ፣ በዘመኑ «የ ዩ.ኔ.ስ.ኮ. ኃላፊ የነበሩት ክቡር አቶ አካለ ወርቅ ሀብተ ወልድ ፓሪስ ለስብሰባ በተገኙበት ጊዜ ሀገራችን በየዓመቱ ፵ሺ ዶላር ለመክፈል በመስማማት ግዴታዋን ስትወጣ በአንፃሩም በአባልነታቸው በርካታ መጽሐፎችን ያገኙ እንደነበር ይመሰክራሉ» ይላል።

[ከመጻሕፍቱ መካከል]
* ማኅደረ ደራስያን

[መገኛዎቹ] ፌስቡክ፡ - https://facebook.com/353856951405810/
[ምንጮቻችን] አልተገለጸም (ወደ ፊት የሚካተት)


ስለሌሎች ደራስያን እዚህ ይወቁ

መጻሕፍት ከየምድባቸዉ ለመምረጥ እዚህ ይግቡ መጻሕፍት ከጠቅላላ ዝርዝር ለመምረጥ እዚህ ይግቡ
የኢትዮጵያ ደራስያን ማኅበር
መገኛችን

ለገሀር፣ አዲስ አበባ

19686

yehaarts@gmail.com

+251 912 944937

ጉርሻ - Bonus

“ከፊደል ሀ፣ ከከተማ የሓ የሚቀድም የለም” ተብሏል፡፡ የአጋዝያን ምድር፣ የግዕዝ ቋንቋም መነሻ፣ የልዕልናችንም መጀመሪያ ነበረች፡፡ በብዙ ጥበብ የተንበሽበሽች፡፡ አሁን እምብዛም ሞቋት የማታድረዋ የሓ፤ የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ ሁነኛ ዋና ከተማ ነበረች።

(2015-2024) © yehaarts