ተክሉ ጥላሁን
[የትዉልድ ቀን] 1970-05-12
[አጭር መግለጫ]
ደራሲ እና አዘጋጅ ተክሉ ጥለሁን ተወልዶ ያደገዉ በአዲስ አበባ ነዉ፡፡ ከትምህርት ቤት ጀምሮ በሚኒሚዲያ እና በተለያዩ አጋጣሚዎች በንቃት እየተሳተፈ ያደገ ሲሆን፣ መደበኛ ስልጠናዉንም በጋዜጠኝነት አግኝቷል፡፡ “ያልሰከነ ዜማ” የመጀመሪያዉ የታተመ መጽሐፉ ሲሆን፤ ከ27 ጊዜ በላይ ታትሞ በሰፊዉ የተነበበለትንና፣ በእዉነተኛ ታሪክ ላይ ተመስርቶ የጻፈዉን “የጭን ቁስል”ን ጨምሮ “የሎጥ መንገድ”፣ “ከስኬት በስተጀርባ”፣ “የስኬት መንገዶች”፣ “ዴዝዴራታ”፣ “የቀን ጨለማ” እና ሌሎች መጽሐፍትን ለኅትመት ብርሐን አብቅቷል፡፡ ለብቻዉ እና ከሌሎች ጋር በመጣመር የጻፋቸዉ እና ያሳተማቸዉ መጽሐፍትም ቀላል የሚባሉ አይደሉም፡፡ ለምሣሌ፡ “ጃንሆይን ማን ገደላቸዉ?” (ከዐቢይ ደምሴና ተሥፋሁን ምትኩ ጋር)፣ “ያልተዘመረላቸዉ” (በአሜሪካ ኤምባሲ ትብብር) ይጠቀሱለታል፡፡ ከዚህ በተጨማሪም ከስድስት በላይ በሆኑ የአማርኛ ፊልሞች ላይ ቀጥተኛ ተሳትፎ ያለዉ ሲሆን (“ዐሥርቱ ቀናት”፣ “እፉዬ ገላ”፣ “አብሳላት” እና ሌሎች)፣ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ ደግሞ በዉጭ ሀገር ቋንቋ የተጻፉ ልዩ ልዩ ቅርጽ ያላቸዉ መጽሐፍትን ወደ አማርኛ ቋንቋ በመመለስ ሂደቱ ላይ ሰፊና ቀጥተኛ ተሳትፎ እያደረገ ይገኛል፡፡
[ከመጻሕፍቱ መካከል] * የጭን ቁስል
[መገኛዎቹ] ፌስቡክ፡ - https://facebook.com/teklu.tilahun
ቴሌግራም፡ - https://t.me/teklu_tilahun
[ምንጮቻችን] https://yehaarts.com
ስለሌሎች ደራስያን እዚህ ይወቁ
መጻሕፍት ከየምድባቸዉ ለመምረጥ እዚህ ይግቡ
መጻሕፍት ከጠቅላላ ዝርዝር ለመምረጥ እዚህ ይግቡ