ታላቁ ጥቁር
[ርዕሥ] | ታላቁ ጥቁር |
[ደራሲ] | ንጉሤ አየለ ተካ |
[አርታዒ] | |
[ምድብ] | ኢ-ልብ ወለድ |
[ዘዉግ] | የኢትዮጵያ ታሪክ |
[አሳታሚ] | አልተገለጸም (ወደ ፊት የሚካተት) |
[የመጀ.ዕትም] | 2010-00-00 |
[አሁን የደረሰበት] | 0ኛ ዕትም |
[ISBN (መለያ)] | አልተገለጸም (ወደ ፊት የሚካተት) |
[የገጽ ብዛት] | 473 |
[የሽፋን ዋጋ] | 335 |
[መሸጫ ዋጋ] | 335 |
| |
[ቅንጭብ]
ሚስተር ሮበርት ስኪነር በዋና ቆንስል ማዕረግ የፕሬዝዳንት ቴዎዶር ሩዝቬልትን መልዕክት ለአጼ ምኒልክ እንዲያደርስ የተላከውን የአሜሪካ ልዑካን ቡድን በመምራት ወደ ኢትዮጵያ ይሄዳሉ የተባለው ጉዳይ በግልፅ ከታወቀ በኋላ በበርካታ አሜሪካውያን ዘንድ ስለ ኢትዮጵያ እና ስለ አጼ ምኒልክ ለማወቅ ከፍ ያለ ጉጉት በማደሩ፣ የአሜሪካ ጋዜጦች ስለ ኢትዮጵያ በብዛት ይጽፉ ነበር። የሮበርት ስኪነር ቡድን ተልዕኮ አሜሪካ ከሰሃራ በታች ወደሚገኝ የአፍሪካ ክልል ይህን የመሰለ የዲፕሎማሲና የወዳጅነት ግንኙነት ለመመስረት መነሳቷ በታሪኳ የመጀመርያ” ነበር። በወቅቱ የኒውዮርክ ሄራልድ ጋዜጣ ስለጉዳዩ ባወጣው ዜና “ይህ ምናልባትም በዲፕሎማሲ ታሪካችን ታይቶ እማይታወቅ የተልዕኮ ጉዞ ነው” ሲል እንደጻፈ ደራሲው በመጽሐፋቸው ጠቅሰውታል።
[ንጉሤ አየለ ተካ ሌሎች መጻሕፍት] * ታላቁ ጥቁር
✓ እዚህ ላይ ይግዙት
ሌሎች መጻሕፍት ይምረጡ