ገ ረ ገ ራ     በማንኛዉም የመጽሐፍ አዟሪና መደብር ይገኛል።     Order4Delivery (እዚሁ ያዝዙ)
ዐውደ ዜና

ሰሞነኛ ወሬዎች፣ አዳዲስ ነገሮች፣ የመርሐ ግብር ጥቆማዎች

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ፷ኛውን ዐመት የአልማዝ ኢዮቤልዮ በዐሉን ማክበር ጀመረ፡፡

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቴአትር ፷ኛውን ዐመት የአልማዝ ኢዮቤልዮ በዐሉን ማክበር ጀመረ፡፡

 ዉብርስት በልስቲ       2015-07-10

ለአዲሱ ዘመናዊ የቴአትር ቤት ግንባታ የተጣለውን የመሰረት ድንጋይ ተከትሎ ፷ኛውን ዐመት የአልማዝ ኢዮቤልዮ እንደሚያከብር የገለጸው አንጋፋው ቴአትር ቤት - ብሔራዊ፡፡ ዋናው በዐል ህዳር ፫፣ ፳፻፰ዓ.ም. እንደሚሆን በተለያዩ ‹ፖስተሮች› የተገለጸ ቢሆንም ቅደመ ዝግጅቶች ግን ከወዲሁ ተጀምረዋል፡፡ አልፎ አልፎ ከሚኖሩት ነጻ የሙዚቃ ድግሶች በተጨማሪ ልዩ ልዩ ጥበባዊ ክንዉኖችም እንደሚቀጥሉ ታውቋል፡፡ ከዚሁ ጋር በተያያዘ፤ በቅድመ በዐሉም ሆነ ከበዐሉ በኋላ የመጀመሪያዎቹ የቴአትር ቤቱ ከያንያንና መስራቾች በብዙ እንደሚታሰቡ የሚጠበቅ ሲሆን ቴአትር ቤቱና የቴአትር ታዳሚዎች በቅርበት የሚወያዩበት መድረክ እንደሚፈጥርም ይታሰባል፡፡

ዜናውን ለማጠናቀር በቴአትር ቤቱ አካባቢ በተዘዋወርንበት ጊዜ ያነጋገርናቸው የቴአትር ተመልካቾችም ‹‹ቴአትር ቤቱ እዚህ እንዲደርስ የደከሙ ቀዳሚዎች በዘጋቢ ፊልም፣ በሙዚቃ፣ በቴአትር እና በሌሎች መንገድ ሊነገርላቸው ይገባል፡፡ በዐሉም ይልቁን የሚደንቀው በዚሁ መልክ ነውና ከወዲሁ እንዲታሰብበት›› ሲሉ አሳስበዋል፡፡

33 ከ 33

ሊያጋሩን የሚፈልጉት መረጃ (የዜና ጥቆማ) ካለዎ ያግኙን

መገኛችን

ለገሀር፣ አዲስ አበባ

19686

yehaarts@gmail.com

+251 912 944937

ጉርሻ - Bonus

“ከፊደል ሀ፣ ከከተማ የሓ የሚቀድም የለም” ተብሏል፡፡ የአጋዝያን ምድር፣ የግዕዝ ቋንቋም መነሻ፣ የልዕልናችንም መጀመሪያ ነበረች፡፡ በብዙ ጥበብ የተንበሽበሽች፡፡ አሁን እምብዛም ሞቋት የማታድረዋ የሓ፤ የመጀመሪያዋ የኢትዮጵያ ሁነኛ ዋና ከተማ ነበረች።

(2015-2024) © yehaarts